አርስተ ዜና -የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቻይና በፕሬዚዳንት ዢ ከፍተኛ አቀባበል ተደረገላቸዉ። ትራምፕ አስደናቂ መሪ ሲሉ ዢ ጂንፒንግን አሞካሽተዋቸዋል። የሁለቱ ሀገራት "የተረጋጋ" ግንኙነት ለዓለም ፋይዳ እንደሚሆን የተናገሩት ዢ ጂንፒንግ በበኩላቸዉ፤ የታይዋን ጉዳይ በአግባቡ ካልተያዘ ግን ግጭት ሊፈጠር ይችላል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።-ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጋር በተያያዘ በዩናይትድ ስቴትስ ከ4 ዓመታት በፊት ኢትዮጵያ ላይ ተጥሎ የቆየው የጦር መሣሪያ ማዕቀብ መነሳቱ ተገለፀ። ዩናይትድ ስቴትስ ኤርትራ ላይ የጣለችዉን ማእቀብ ለማንሳት እያሰበች እንደሆን ያስታወቀችዉ በዚሁ ሰሞን እንደሆን የሚታወስ ነዉ።