--መቀመጫዉን ዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ያደረገዉ፤ የሳይበር ደህንነት ኩባንያ ባካሄደዉ የተሳሳተ የይዘት ማሻሻያ በመላው ዓለም ከፍተኛ መስተጓጎል አስከተለ። የአዉሮፕላን በረራዎች፤ የንግድ ተቋማት እና ሌሎች ስራዎች ለሰዓታት ተስተጓጎለዉ ነበር። --የኬንያ ፍርድ ቤት ፖሊስ በዋና ከተማዋ ናይሮቢ እና አካባቢዋ ላይ ፀረ-መንግስት ተቃውሞዎችን ለማገድ የወሰነዉን እርምጃ፤ ፍርድ ቤት አገደ።--የቀድሞ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ፤ በእጩነት መመረጣቸዉን በሙሉ ፍላጎት ተቀበሉ። በሌላ በኩል የቀድሞዉ ባራክ ኦባማ እና ናንሲ ፔሎሲ፤ ጆ ባይደን ለዳግም ምርጫ ለመወዳደር በቂ አቅም የላቸዉም ሲሉ ጥርጣሪያቸዉን ገልፀዋል።