አርስተ ዜና፤--የጀርመኑ መራሔ መንግስት ፍሬድሪክ መርስ የጀርመን መንግስት ከዮርዳኖስ ጋር በመተባበር ለጋዛ የሰብአዊ ርዳታ በአየር ላይ ለማድረስ በዝግጅት ላይ መሆኑን ተናገሩ። በፍልስጤም ግዛት ውስጥ የሚታየዉ ከፍተኛ የምግብ እና የውኃ እጥረት ለአስከፊ ረሃብ እንዳይዳርግ ሲሉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅቶች አስጠንቅቀዋል።--በአገሪቱ የሚገኙ ሁሉም የፖለቲካ ኃይሎችና ባለድርሻ አካላት አገራዊ መግባባትንና ዘላቂ መፍትሔዎችን እንዲያመጡ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ጠየቀ። ታይላንድ እና ካምቦጂያ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ ስምምነት ላይ ከደረሱ በኋላ ስምምነቱ ተጥሶ ውጊያ ማገርሸቱ ተሰማ።