-የባንግላዴሽ የጠ/ሚ ሼክ ሃሲና በህዝባዊ ትግል ከስልጣን ለቀቁ። የ 76 ዓመትዋ ሃሲና፤ ምናልባትም ወደ ህንድ ሳይሰደዱ አልቀረም። -በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ በመሬት ናዳ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡ በአደጋዉ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ሳይጨምር አይቀርም።-የደቡብ አፍሪቃ ፖሊስ ጆሃንስበርግ ዉስጥ ታፍነዉ ተይዘዉ የነበሩ 90 ኢትዮጵያዉያን ስደተኞችን ነፃ አስለቀቀ። ፍልሰተኞቹን ያፈኑት ሁለት የሰዎች አዘዋዋሪ ተጠርጣሪዎች ተይዘዋል።-ማሊ ከዩክሬይን ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አቋረጠች። የማሊ ዩክሪን አማፅያኑ ባደረሱት ጥቃት እጇ አለት በሚል ነዉ። ዩክሬይን የማሊ እርምጃን ኮንናዋለች።