--የአፍሪቃ ሕብረት በኢትዮጵያ መንግሥትና በህወሓት መካከል ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ የተፈረመውን የፕሪቶሪያ ስምምነት አፈፃፀም ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ መገምገም ጀመረ።
የተመድት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ዛሬ የጀመረዉን የረመዳን ጾምን በማስመልከት በእስራኤል-ሀማስ መካከል ጋዛ ሰርጥ ዉስጥ የሚካሄደዉ ጦርነት ብሎም የሱዳኑ ግጭት እንዲቆምና እርቅ እንዲወርድ ጥሪ አስተላለፉ።
--በዓለማችን በጦር መሳርያ ንግድ ቀዳሚዋ የሆነችዉ ዩናይትድ ስቴትስ ዘንድሮም ቀዳሚዉን ስፍራ መቀጠልዋን ዓለም አቀፍ የሰላም ምርምር ተቋም አመለከተ። ሁለተኛዋ አገር ፈረንሳይ ነች ተብሏል። ሩስያ ወደ ሦስተኛ ደረጃ ዝቅ ማለትዋም ተመልክቷል።