አርስተ ዜና፤
-ፈረንሳዊትዋ የቀኝ አክራሪ ፓርቲ መሪ ማሪን ለ ፔን «ራሊ ናሽናል» በተባለዉ ፓርቲያቸዉ በኩል የአውሮፓ ፓርላማ ገንዘብን አላግባብ በመጠቀም ጥፋተኛ ተባሉ። አራት ዓመት እስር የተፈረደባቸዉ ላፔን ሁለት ዓመት እግራቸዉ ላይ መቆጣጠርያ ታስሮ የቁም እስረኛ እንደሚሆኑ ተነገረ።-በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አበዶንጎሮ ወረዳ ውስጥ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት ጸጥታ ሐይሎችን ጨምሮ የ 21 ሰዎች ህይወት ጠፋ።-የአሜሪካዉ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሩስያዉ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አቋም እጅግ መበሳጨታቸዉን ገለፁ። ፑቲን በበኩላቸዉ በጽ/ቤታቸዉ በኩል ለትራምፕ በሬ ክፍት ነዉ ብለዋል።