የመጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
የቀድሞ የሶማሌ ክልል ርዕሠ መስተዳድር አብዲ መሐመድ ዑመር እና የቀድሞ የሜቴክ የበላይ ሃላፊ ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው ከእስር ተለቀቁ ።
አሸባብ መቅዲሾ ውስጥ በሚገኘው «ሳይ» በተባለው በዚሁ ሆቴል ላይ ትናንት ምሽት በደረሰው ጥቃት የአሸባብ ሚሊሽያዎችን ጨምሮ ቢያንስ ስምነት ሰዎች ተገደሉ። 18 ሰላማዊ ሰዎችና 9 ወታደሮች ቆስሉ።
በሩስያ ለሦስት ቀናት የሚካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ዛሬ ተጀምሯል። ምርጫው ሩስያ ከዩክሬን በገነጠለቻቸው ግዛቶችም ጭምር እየተካሄደ መሆኑ ተገልጿል። የ71 ዓመቱ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ለአምስተኛ የስልጣን ዘመን ነው የሚወዳደሩት።