ሚያዝያ 7 ቀን፣ 2018 ዓ.ም. ረፋድ ላይ ማንነታቸው ባልታወቁ እና ሲቪል የለበሱ በተባሉ ሰዎች ከሥራ ቦታው የተወሰደው የአዲስ ስታንዳርድ ማኔጂንግ ኤዲተር ሚሊዮን በየነ እስካሁን ያለበት ቦታ እንዳልታወቀ ተገለፀ። -ትራምፕ «እስራኤል እና ሊባኖስ ለ10 ቀናት የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ደርሰዋል»-የኬንያ ፍርድ ቤት አንድ ቻይናዊ ህገ-ወጥ የጉንዳን አዘዋዋሪ ላይ የአንድ ዓመት እስራት ፈረደ።-የአፍሪቃ ጉብኝታቸዉን የቀጠሉት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ አሥራ አራተኛ በካሜሩን የሚገኙ ባለስልጣናት ሕሊናቸውን እንዲመረምሩ እና "የሙስና ሰንሰለትን" እንዲሰብሩ ጥሪ አቀረቡ።