አርስተ ዜና
--ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪቃ ሃገራት ያሉ የእናቶችና የህጻናትን ጤና ለማሻሻል ያለመ የ500 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ማሰባሰብያ ዛሬ አቡዳቢ ላይ ጀመረ። የተሰበሰበዉ ገንዘብ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ኢትዮጵያ፣ ጋና፣ ጨምሮ ከ10 አፍሪቃ ሀገራት ጋር አጋርነት ለመፍጠር ያለመ ነዉ።--ዓለምአቀፉ ማህበረሰብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሰብአዊ መብቶችን መጠበቅ አልቻለም ሲል የዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርግት አምነስቲ ኢንተርናሽናል ከሰሰ።--የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለሁለተኛ ጊዜ ስልጣን ከያዙ ዛሬ 100 ኛ ቀናቸዉን ደፈኑ።