አርስተ ዜና፦
--እስራኤል ትናንት ሃሙስ በጋዛ ከተማ አዲስ የምድር ጦር ጥቃት ሰነዘረች። ጥቃቱ ትልቁ የጋዛ ከተማን ለመቆጣጠር የመጀመሪያ ምዕራፍ ነዉ ተብሏል።--የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር የሀገሪቱን የፋይናንስ ሚንስትር ከስልጣን አሰናበቱ።--ኢትዮጵያ ውስጥ ጦርነት ግጭትና ኃይል የቀላቀለ ውጊያ እንዲቆም የሚጠይቅ ጉባኤ ሊካሄድ መሆኑን የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ም/ቤት አስታወቀ።--በኒው ዮርክ የሚገኝ የይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት በዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በድርጅታቸው ላይ የተጣለውን 500 ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ቅጣት ውድቅ አደረገ። ትራምፕ የፍርድ ቤቱን እርምጃ ድል ብለዉታል።