-የኢትዮጵያ መንግሥትን በነፍጥ የሚወጉ ኃይላት በሐገሪቱ ብሔራዊ የምክክር ሒደት እንዲካፈሉ ለተደረገላቸዉ ጥሪ መልስ አለመስጠታቸዉን የምክክር ኮሚሽን አስታወቀ።ለታጣቂዎቹ ኃይላት ጥሪዉ የተደረገበትን መንገድና ጥሪዉ ሥለመድረስ አለመድረሱ ግን የኮሚሽኑ ባለሥልጣናት አልጠቀሱም።-----ግብፅ ለሶማሊያ የጦር መሳሪያ ማስታጠቅ ጀመረች።መሳሪያ የጫኑ ሁለት የግብፅ የጦር አዉሮፕላኖች ትናንት ሞቃዲሾ ማረፋቸዉን ዲፕላቶች አስታዉቀዋል።ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር ወደብ ለመኮናተር ከተስማማች ወዲሕ የሞቃዲሾና የካይሮ ፍቅር ፀጥንቷል