DW Amharic
--በኢንዱስትሪ የበለጸጉት የቡድን ሰባት አባል ሐገራት የመሪዎች ጉባዔ ዛሬ በጣልያን ጀመረ። የሃገራቱ የጉባዔ ዋንኛ ርዕስ ዩክሬንን በጦር መሳሪያና በገንዘብ ድጋፍ ማጠናከር ነዉ። በጋዛ እየተካሄደ ያለዉ ጦርነት፤ ከቻይና ጋር ውጥረት የበዛበት የንግድ ግንኙነትና የፍልሰት ጉዳይ ጉባኤዉ ይመክርባቸዋል።
--ገጣሚ በላይ በቀለ ወያ በገንዘብ ዋስ ከእሥር ተለቀቀ። ገጣሚዉ ወጣት ባሕር ዳር ከተማ ማረሚያ ቤት ለ 11 ወራት ታሥሮ ቆይቷል።
--በየመን የባሕር ዳርቻ በደረሰ የጀልባ አደጋ ቢያንስ 49 ሰዎች መሞታቸዉ ተሰማ። በጀልባዉ ላይ፤ 115 ሶማልያዉያን እና 145 ኢትዮጵያዉያን ተሳፍረዉ ነበር።