አርስተ ዜና፤ -የኤርትራ ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ግብፅን ለ5 ቀናት ለመጎብኘት ዛሬ ከአስመራ ወደ ካይሮ ተጓዙ። ኢሳያስ ግብፅን የሚጎበኙት የግብጹ ፕሬዝደንት አብዱልፈታሕ አል ሲሲ ባደረጉላቸዉ ግብዣ ነዉ።-በኢትዮጵያ ከመንግሥት ጋር ይሰራል የሚል ትችት የሚቀርብበት የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፤ ኢዜማ ፓርቲ፤ ገዥዉ ብልፅግና የመንግሥት ሠራተኞችን በግዳጅ የፓርቲ አባል የማድረግ እርምጃን እንዲያቆም ጠየቀ።-የተመድ በሱዳን ዳርፉር የምትገኘውን ኤል-ፋሸር ከተማን የተቆጣጠረዉን በሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ርምጃ በጥብቅ አወገዘ።