አርስተ ዜና፤
--በተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች የሚደገፈው የደቡብ የሽግግር ምክር ቤት የተሰኘው የደቡብ የመን ተገንጣይ ቡድን መፍረሱን አስታወቀ። የቡድኑ መሪ ከቀናት በፊት ከየመን በባሕር ወደ ሶማሌላንድ በመጓዝ ከዚያ በአውሮፕላን ወደ አቡዳቢ መግባታቸውን ሳውድ አረቢያ መግለጻ ይታወሳል። --ትግራይ ክልል በኢኮኖሚ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ እና ፀጥታ ስጋት ዉስጥ መሆንዋ ተነገረ።--የአዲሱ የቬንዙዌላ ጊዜያዊ አስተዳደር በማዶሮ ዘመን እስር ላይ የነበሩ በርካታ ታዋቂ የፖለቲካ እስረኞችን ለቀቀ።--ኢራን ዉስጥ በተከሰተዉ የኑሮ ውድነት ምክንያት የተነሳዉ ፀረ መንግሥት ተቃዉሞ ዛሬም ተባብሶ እንደቀጠለ ነዉ።