አርስተ ዜና፤
-የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች አዋጅን ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ ከ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በፊት እንዳይፀድቅ ውትወታ እያድረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ዛሬ አስታወቀ።
-ከያዝነዉ የፈረንጆቹ ዓመት 2026 መጀመርያ ጀምሮ በሁለት ወራት ጊዜ ዉስጥ ከአፍሪቃዉ ቀንድ አካባቢ ተነስተዉ ሜዲትራኒያን ባህር አቋርጠው ወደ አውሮጳ ለመግባት የሞከሩ ቢያንስ 606 ስደተኞች በባህር ሰጥመዉ መሞታቸውን IOM አስታወቀ።-ሩሲያ በዩክሬን ላይ ጦርነት ወረራ የጀመረችበት አራተኛ ዓመት ዛሬ በዩክሬይን መዲና ኪይቭ ላይ ታስቦ ዋለ። የአዉሮጳ ኅብረት አባል ሃገራትና ኔቶ ለዩክሬይን ጠንካራ አጋርነታቸዉን አሳይተዋል።