የየካቲት 22 ቀን 2016 ዓ.ም. አርዕሰተ ዜና
-በባሕርዳር ዛሬ ጠዋት በከተማው ቀበሌ 14ና በተለምዶ ዓባይ ማዶ በተባሉት የከተማው አካባቢዎች የተኩስ ልውውጥ እንደነበር ነዋሪዎቹ ለዶቼቬለ ተናገሩ፡፡
-ባለፈው መስከረም በጀርመንዋ ሽቱትጋርት ከተማ በተካሄደ የኤርትራውያን ድግስ ላይ በተነሳው ብጥብጥ መንስኤ የሽቱትጋርት ፍርድ ቤት የ29 ዓመት ኤርትራዊ ወጣት ላይ የሦስት ዓመት ከ9 ወራት እሥራት መበየኑን የፍርድ ቤቱ ቃል አቀባይ ተናግረዋል።
-ትናንት የእስራኤል ወታደሮች ርዳታ ለመውሰድ ይሞክሩ በነበሩ ሲቪል ፍልስጤማውያን ላይ በከፈቱት ተኩስ በርካታ ፍልስጤማውያን መገደላቸው ከዓለም ዙሪያ ውግዘት ገጥሞታል።