አርዕስተ ዜና፦ ሽንሌ፥ ኢሰመኮ በአፋር እና ሶማሌ አዋሳኝ አካባቢዎች ግጭት ማገርሸቱ አሳስቦኛል አለ፤ የሩስያ ፕሬዚደንት ቭላድሚር ፑቲን ከዩክሬን ጋ ለመደራደር ሀገራቸው በቁጥጥሯ ስር ካዋለቻቸው ግዛቶች የዩክሬን ጦር ሙሉ ለሙሉ መውጣትን እንደ ቅድመ ሁኔታ አስቀመጡ፤ የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) ዋና ጸሐፊ ዬንስ ስቶልተንበርግ በዩክሬን ፍትሐዊ እና ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ሩስያ የመስፋፋት ፍላጎቷን ልትገታ ይገባል አሉ፤ የአውሮጳ ሃገራት እግር ኳስ ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ ዛሬ ማታ ሙይንሽን ውስጥ የዘንድሮ አዘጋጇ ጀርመን ስኮትላንድን ትገጥማለች