አርዕስተ ዜና
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ካቢኔ ዛሬ ወደ ፓርላማ የመራው የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ማሻሻያ ህወሓት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሕጋዊ ሆኖ እንዲመዘገብ መንገድ የሚከፍት ነው።
በደቡብ አፍሪቃው ምርጫ የድምጽ ቆጠራ ኤ ኤን ሲ ከ50 በመቶ በታች ድምጽ ማግኘቱ ከታወቀ በኋላ ሌሎች ፓርቲዎች ዛሬ የጥምረት ንግግር ለማካሄድ ዝግጅት መጀመራቸው ተሰማ ።
የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቀረቡባቸው 34 ክሶች በሙሉ ጥፋተኛ በመባላቸው ላይ የተለያዩ መንግስታትና የፓርቲዎች መሪዎች አስተያየቶች እየተሰጡ ነው።