አቶ ዮሐንስ ቧያሌው፣ ዶክተር ካሳ ተሻገር እና አቶ ክርስትያን ታደለን ጨምሮ 14 በእሥር ላይ የሚገኙ ታዋቂ ፖለቲከኞች ከተያዙበት ጊዜ ጀምሮ «አካላዊ ፣ ሞራላዊ እና ሥነ ልቦናዊ ጥቃት» እየተፈፀመባቸው መሆኑን ገለጡ፤
የዩጋንዳ የረዥም ዘመን አምባገነን መሪ ፕሬዚደንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ጄኔራል ልጃቸውን የሀገሪቱ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር አድርገው ሾሙ ፤
የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት በጋዛ አስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ስትል ዩናይትድ ስቴትስ ያቀረበችውን ረቂቅ ዛሬ ሳያፀድቅ ቀረ፤
ሩስያ በስምንት ሚሳይሎች የዩክሬን ግዙፉን ዲኒፕሮ የኃይል ማመንጫ ተቋም ዛሬ ደበደበች ።