አርዕስተ-ዜና
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እስካሁን የሠላም ሚንስትር የነበሩትን ብናልፍ አንዷለምን ሽረዉ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሐን ባለሥልጣን የበላይ ኃላፊ የነበሩትን መሐመድ ኢድሪስን
በሠላም ሚንስትርነት ሾመዋል።
በምዕራብ ኦሮሚያ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ሱሉላ ፍንጫ ወረዳ የሚገኘው የፍንጫ ስኳር ፍብሪካ የአገዳ ምርት ትናንት መቃጠሉን የፋብሪካዉ ሠራተኞችና ነዋሪዎች አስታወቁ።
በምግብ ቀውስ ውስጥ በሚገኘው በጋዛ ሰርጥ በአንድ ዳቦ ቤት ውስጥ በተፈጠረ ግፍያ ሁለት ህጻናትና አንዲት ሴት ታፍነው መሞታቸውን የህክምና ባለሥልጣናት ተናገሩ።