አርዕስተ ዜና
*በአሳሳች የሥራ ዕድል ተታለው ወደ ምያንማር የሄዱ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በርካታ የውጭ አገራት ዜጎች ብርቱ ሥቃይ እንደሚደርስባቸው የፈረንሣይ ዜና አገልግሎት ዘገበ ።
*የኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚደንት ፌሊክስ ሺሴኬዲ ድጋፍ ፍለጋ ከአገር ውጪ ባሉበት በዛሬው ዕለት በሩዋንዳ የሚደገፈዉ M23 አማፂ ቡድን ሁለት ተጨማሪ ከተሞችን ተቆጣጠረ ።
*የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬሽ ሱዳን ውስጥ የጦር መሣሪያ ፍሰት እንዲቆም ጥሪ አስተላለፉ ።