የግንቦት 11 ቀን 2017 ዓ.ም አርዕስተ ዜና
የጤና ባለሞያዎች የሥራ ማቆም አድማ ዛሬም በአንዳንድ ሆስፒታሎች መቀጠሉን የንቅናቄው አስተባባሪዎች ለዶቼቬለ ተናግረዋል። አንዳንዶቹ ደግሞ በከፊል ሥራ ላይ እንደሆኑ ገልጸዋል።
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ነታንያሁ እስራኤል መላ ጋዛን እንደምትቆጣጠር አስታወቁ። ነታንያሁ በዘመቻው ሀማስ እስካሁን ጋዛ ውስጥ የያዛቸውን 58 ታጋቾችን ማስለቀቅና በሚሊሽያዎች ላይ ሙሉ ድል መቀዳጀትን እናሳካለን ብለዋል።
ብሪታንያ ከአውሮፓ ኅብረት አባልነት ከወጣች ከአምስት ዓመት በኋላ ከኅብረቱ ጋር አዲስ የአጋርነት ስምምነት ዛሬ ተፈራረመች።