-በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዉስጥ የኤሌክትሪክ ኃይልና ዉኃ ለተከታታይ ሳምንታት በመቋረጡ ሕዝብ ለችግር መጋለጡን ነዋሪዎች አስታወቁ።ዉኃና መብራቱ የተቋረጠዉ አንድ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ በመቃጠሉ እንደሆነ ባለሥልጣናት አስታዉቀዋል።---የእስራኤል መንግሥት የጋዛ ፍልስጤሞችን መግደል፣ማሰቃየትና ማስራቡን እንዲያቆም የሚደረግበት ግፊት እንደቀጠለ ነዉ።የእስራኤል ወታደሮች የምዕራባዊ ዮርዳኖስ ወንዝ ዳርቻን በሚጎበኙ ዲፕሎማቶች ላይ ተኩስ መክፈታቸዉን አዉሮጶች አዉግዘዉታል።---የሩሲያዉ ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ጦራቸዉ በቅርቡ መልሶ የተቆጣጠራትን የኩርስክ ግዛትን ጎበኙ።