የግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ (ኦፌኮ) ለመንግሥት አቅርቦት የነበረው ጥያቄ አጥጋቢ ምላሽ ባለማግኘቱ በምርጫው ተሳትፎው እጅግ የተቀዛቀዘ እንዲሆን ማድረጉን አስታወቀ ።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የትምህርት ቢሮ በክልሉ የ2018 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ከታቀደው አንድ ወር ቀደም ብሎ እንደሚያበቃ አስታወቀ።
ባለፉት 3 ሳምንታት ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ፣ ዩጋንዳ ወይም ደቡብ ሱዳን የነበሩ አሜሪካውያን ጠለቅ ላለ ምርመራ ፣በዋሽንግተን ዳላስ አውሮፕላን ማረፊያ በኩል ብቻ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ እንዲገቡ የአሜሪካን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳሰበ ።