DW Amharic እስራኤል በደቡብ ጋዛ በምትገኘው የራፋሕ ከተማ እያካሄደችው ባለው ጥቃት 35 ፍልስጤማውያን መገደላቸውን የጋዛ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታወቀ። -በጀርመን በሕዝብ በተመረጡ ፖለቲከኞች ላይ እየደረሰ ያለው የአመጽ ጥቃት እንዳሳሰባቸው የጀርመን ፕረዚዳንት ገለጹ። ፕረዚደንቱ ይህን የገለጹት ጀርመን የምትተዳደርበትን መሰረታዊ ሕግ የጸደቀበትን 75ኛ ዓመት ዛሬ በበርሊን ከተማ በተከበረበት መድረክ ነው።-ሩስያ ያለብንን የአየር መቃወምያ እጥረት እንደበጎ ዕድል በመውሰድ ጭካኔ የተሞላበት ጥቃት እየፈጸመችብን ነው ሲሉ የዩክሬይን ፕረዚደንት ቮሎደሚር ዘለንስኪ አስታወቁ።