ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎና ኡጋንዳ በተጨማሪ 10 የአፍሪካ ሐገራት የኢቦላ ቫይረስ ሥርጭት እንደሚያሰጋቸው የአፍሪካ የበሽታዎች መከላከያና መቆጣጠሪያ ድርጅት አስታወቀ። ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን ላይ ዳግም ጦርነት የምታውጅ ከሆነ ብርቱ አጸፋዊ ምላሽ እንደምትሰጥ ኢራን አስጠነቀቀች። በሰሜን ቻይና በምትገኝ የሻንዚ ግዛት በአንድ የከሰል ማዕድን ማውጫ ትላንት ባጋጠመ ፍንዳታ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ቢያንስ 90 መድረሱን ተሰማ። ዩክሬይን በሩስያ ቁጥጥር ሥር በሚገኘው እና የቀድሞ ግዛቷ በነበረው ሉጋንስክ ከተማ ፈጸመችው በተባለ የድሮን ጥቃት 18 ሰላማዊ ሰዎች ሲሞቱ 48 መቁሰላቸውን የአካባቢው የሩስያ ገዢ አስታወቁ።