የዓለም ዜና

የግንቦት 19 ቀን 2016 ዓ.ም. የዓለም ዜና


Listen Later

እስራኤል ትናንት ምሽት ራፋ ላይ ባካሄደችው የአየር ጥቃት ቢያንስ 35 ፍልስጤማውያን መገደላቸው ተሰማ። ጥቃቱ የተፈጸመው በጦርነቱ የተፈናቀሉ ወገኖች በተጠለሉበት ስፍራ መሆኑ ትኩረት ስቧል።
በእስራኤል እና ግብጽ አዋሳኝ ድንበር አካባቢ የተኩስ ልውውጥ አንድ የግብጽ ድንበር ጠባቂ ወታደር ተገደለ። ሁለቱም ሃገራት ጉዳዩን እየመረመሩ መሆኑን አስታውቀዋል።
ባለፈው ሳምንት ዓርብ በተከሰተ የመሬት መደርመስ ከሁለት ሺህ በላይ ሕዝብ ከእነሕይወቱ ሳይቀበሩ እንዳለቀረ የፓፓዋ ኒው ጊኒ መንግሥት አመለከተ።
የጀርመን ፍርድ ቤት ለሩሲያ በመሰለል በተጠረጠረ ወታደራዊ መኮንን ላይ የሦስት ዓመት ከመንፈቅ እስራት ፈረደ።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW