የዓለም ዜና

የግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ.ም. የዓለም ዜና


Listen Later

የግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር በተያያዘ ከታሰሩ ከ 80 በላይ ሰዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ። ዛሬ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ከቀረቡት ውስጥ ጋዜጠኞች፣ የቤተ ክርስትያን ሰዎች እና ፖለቲከኞች ይገኙበታል ተብሏል።
የዘንድሮው የዶቼቬለ የንግግር ነጻነት ሽልማት ለሩስያዊቷ ዩልያ ናቫልናያና ሟቹ ባለቤታቸው አሌክሲ ናቫልኒ ለመሠረቱት በምህፃሩ FBK ለተባለው ፀረ ሙስና ድርጅታቸው ዛሬ ተሰጠ።
አንድ «አማራጭ ለጀርመን» የተባለው የጀርመን ፓርቲ ፖለቲከኛ በደቡብ ምዕራብ ጀርመንዋ በማንሀይም ከተማ ትናንት ጥቃት እንደተፈጸመባቸው ፓርቲያቸውና ፖሊስ አስታወቁ።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW