የግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
የትግራይ ክልል ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ወደ ትግራይ ለጉብኝት የሚጓዙ ቱሪስቶችን ጨምሮ በተለያየ ስራ የተሰማሩ የውጭ ዜጎች ወደ ክልሉ እንዳይጓዙ በኤርፖርቶች ክልከላ እየተደረገባቸው ነው ሲል አስታወቀ ።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአራት ቀናት የመካከለኛው ምሥራቅ ጉብኝታቸውን ዛሬ በሳዑዲ አረብያ ጀመሩ።
የጀርመን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር የጀርመን ንጉሳዊ አገዛዝ «Kingdom of Germany» የተባለውን ቀኝ ጽንፈኛ ቡድን ዛሬ አገዱ። የቡድኑ መሪ የተባሉ 4 ሰዎች መያዛቸውንም አስታውቀዋል።