የግንቦት አንድ ቀን አርዕስተ ዜና
ምያንማር ውስጥ ለዘጠኝ ወራት "በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ" የቆዩ 82 ኢትዮጵያውያን ዛሬ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ። ሌሎች 41 ኢትዮጵያውያን ደግሞ በዚህ ሳምንት ረቡዕ ሀገራቸው ገብተዋል።
የሱዳን የወደብ ከተማ ፖርት ሱዳን ዛሬ ለ6ተኛ ተከታታይ ቀን በድሮን መመታትዋን የሱዳን ጦር ምንጮች አስታወቁ። ምንጮቹ ለጥቃቱ ከሚያዚያ 2015 ዓ.ም. አንስቶ ከሱዳን ጦር ጋር ውጊያ የሚያካሂደውን የፈጥኖ ደራሹን ኃይል ተጠያቂ አድርገዋል።
የእስራኤል ጦር ከየመን የተወነጨፈ ሚሳይል ዛሬ መትቶ መጣሉን አሳወቀ። ሚሳይሉን አስወንጭፊያለሁ ሲል ወዲያውኑ ኃላፊነቱን የወሰደ ግን የለም።