የዓለም ዜና

የህዳር 12 ቀን ቀን 2017 የዓለም ዜና


Listen Later

የኢትዮጵያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለ2017 ተጨማሪ 582 ቢሊዮን ብር ገደማ በጀት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲቀርብ ወሰነ። የቀድሞው የትግራይ ኃይሎች አባላት የነበሩ ከ300 በላይ ተዋጊዎች የጦር መሣሪያዎቻቸውን ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አስረከቡ። ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ኬንያ ከሕንዱ አዳኒ ግሩፕ ጋር የናይሮቢ የአውሮፕላን ማረፊያን ለማስፋፋት እና የኃይል መሠረተ-ልማት ለመገንባት የያዘችውን ዕቅድ ሰረዙ። ዓለም አቀፉ የጦር ወንጀሎች መዳኛ ፍርድ ቤት የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ፣ የቀድሞ መከላከያ ሚኒስትራቸው ዮቭ ጋላንት እና የሐማስ ወታደራዊ አዛዥ ሞሐመድ ዲይፍ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣ።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW