ናይጄሪያ የሽብር እንቅስቃሴ በገንዘብ ይደግፋሉ ያለቻቸውን 44 የቦኮ ሐራም አባላት እስከ 30 ዓመታት በሚደርስ እስራት ቀጣች። በጋዛ ሕጻናትን ጨምሮ ውኃ ለመቅዳት በመጠባበቅ ላይ የነበሩ 10 ፍልስጤማያውን በተፈናቃዮች መጠለያ ውስጥ በእስራኤል የአየር ጥቃት መገደላቸውን የግዛቲቱ የሲቪል ሰዎች ደህንነት ጥበቃ ኤጀንሲ አስታወቀ። የሰሜን ኮሪያ መሪ ኪም ጆንግ ዑን ሩሲያ በዩክሬን ያለውን ግጭት ለመፍታት የምታደርገውን ጥረት ሀገራቸው “ያለ ምንም ቅድመ-ሁኔታ ለመደገፍ” ዝግጁ እንደሆነች ማረጋገጫ ሰጡ። ፕሬዝደንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ ባለፈው አንድ ሣምንት ብቻ ሩሲያ በ1,800 ድሮኖች በዩክሬን ላይ ጥቃት እንደሰነዘረች ተናገሩ።