-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዎላይታ ዞን ምክር ቤት የዞኑን ከፍተኛ ባለሥልጣናት ሽሮ አዳዲስ ሾሟል።በዞኑ የሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች ሹም ሽሩን የሕዝቡን ጥያቄ ለመሸፈን ያለመ በማለት ተችተዉታል።-ሰሜናዊ ጋዛ ዉስጥ የሸመቁ የፍልስጤም ደፈጣ ተዋጊዎች አምስት የእስራኤል ወታደሮችን ገደሉ፤ ሌሎች ሁለት አቆሰሉ።የእስራኤል ጦር በበኩሉ ሊባኖስ ዉስጥ አንድ የሐማስ ከፍተኛ ባለሥልጣን መግደሉን አስታዉቋል።-ኢራን የኑኩሌር መርሐ ግብሯን በተመለከተ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር የጀመረችዉን ድርድር ለመቀጠል ጥያቄ አለማቅረቧን አስታወቀች።የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ትናንት ኢራን ድርድሩ እንዲቀጥል ጠይቃለች ብለዉ ነበር