የሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓም አርዕስተ ዜና
-«መንግስት የዜጎችን ሰላምና ደህንነት የማስጠበቅ ሕጋዊ ግዴታውን ሊወጣ ይገባል!» ሲል ኢሰመጉ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አሳሰበ ።«በዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ግድያዎች፣ እገታና አፍኖ መሰወር በሀገራችን በአሳሳቢ ደረጃ እየተስፋፋ ያለ ጉዳይ» ነው ያለው ኢሰመጉ ለመፍትኄው ግን የሚመለከታቸው አካላት ዳተኛ መሆናቸውን ጠቁሟል ።
-ሳዑዲ አረብያ ዛሬ በአደንዛዥ እጽ ዝውውር የተወነጀሉ ሁለት ሰዎችን በሞት መቅጣትዋን የሀገሪቱ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የአውሮጳ ኅብረት ኮሚሽን ኮሚሽነር ኢርዙላ ፎን ዴር ላየን ዛሬ ለሁተኛ የሥልጣን ዘመን ተመረጡ።