-የኢትዮጵያ የፌደራል ፖሊስ «አደገኛ የሰዉ አዘዋዋሪ ወንጀለኛ» ያለዉን 17 አባላት ያሉት መረብን መበጣጠሱን አስታወቀ።---የዓለም የረሐብተኞች ቁጥር አምና ለሶስተኛ ተከታታይ ዓመት መቀነሱን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታወቀ።የረሐብተኛዉ ቁጥር ቢቀንስም የዓየር ንብረት መዛባትና የንግድ መደናቀፍ የረሐብተኛዉን ቁጥር እንደገና ሊያንረዉ ይችላል።-ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን የገጠሙት ጦርነት የባብ ኤል መንደብን መስመርም አዘግቷል።የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ ተፋላሚዎች የሲቢል ተቋማትን እንዳይመቱ ተማፅነዋል።የአሜሪካ ፕሬዝደንት ግን የኢራንን ድልድዮችና የነዳጅ ተቋማት ለማዉደም እየዛቱ ነዉ።