የሐምሌ 17 ቀን 2017 ዓ.ም አርዕስተ ዜና
ትናንት ከሰዓት በኋላ አዲስ አበባ ውስጥ የጣለው ከባድ ዝናብ ያስከተለዉ ጎርፍ በንብረትና በግንባታ ሥራ ላይ ጉዳት ማድረሱን ነዋሪዎችና የዓይን ምሥክሮች አስታወቁ። የአዲስ አበባ አስተዳደር መግለጫ ሥለደረሰዉ ጉዳት ምንም ያለዉ ነገር የለም።
የኬንያ የሥርዓታዊ ጉዳይ ባለሥልጣን በቅርብ ጊዜው የኬንያው ተቃውሞ 65 ሰዎች መገደላቸውን አስታወቀ። መሥሪያ ቤቱ ፖሊስ በተቃውሞ ሰልፎች ከመጠን ያለፈ ኃይል ተጠቅሟል ብሏል።
ሀማስ የመጨረሻ ያለውን የተኩስ አቁም ምክረ-ሀሳብ ዛሬ በአደራዳሪዎች በኩል ለእስራኤል መላኩን አረጋገጠ።