DW Amharic
-በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የሟቾችን አስክሬን የማፈላለጉ ሥራ ማብቃቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት አስታወቀ ፡፡-የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የህወሃት አመራሮችን ኮነነ። ጊዚያዊ አስተዳደሩ የህዝባዊ ወያነ ሀርነት ትግራይ /ህወሓት/ አመራሮችን የኮነነው፤ በሙስና እና በተደራጀ የማዕድን የመሬት ዘረፋ ፣ በመሳሪያ ንግድ እና በህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ነው።-የሱዳን ወታደራዊ መሪ ጄኔራል አብደል ፋታህ አል-ቡርሃን የግድያ ሙከራ ተፈጸመባቸው።-የሃማስ መሪ እስማኤል ሃኒዬህ ኢራን ውስጥ ከጠባቂያቸው ጋር ተገደሉ።