በአዲስ አበባ ከተማና ኦሮሚያ ክልል የብር አቅም መዳከምን ተከትሎ በሸቀጦች ላይ ዋጋ ጭማሪ ያደረጉ በርካታ የንግድ ድርጅቶች መዘጋታቸው ተገለጸ።
በጸጥታ ችግር ምክንያት ለፈተና በሄዱበት ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ለሁለት ሳምንታት ያህል መቆየት የተገደዱት ከ400 በላይ ተማሪዎች ትናንት ማምሻውን ወደ ቤተሰቦቻቸው መመለሳቸው ተሰማ።
የናይጀሪያ ፖሊስ በሀገሪቱ የተባባሰውን የዋጋ ንረትና የአስተዳደር ችግር በመቃወም አደባባይ ከወጡ ሰልፈኞች ጋር ፍጥጫ ገጥሟል።
ትናንት ለተገደሉት የሃማሱ መሪ በኢራን ብሔራዊ የአስክሬን ሽኝት ሥረዓት ተከናወነ። አዲሱ የኢራን ፕሬዝደንት መንግሥታቸው ለሃማስ የሚያደርገው ድጋፍ ይጨምራል ብለዋል።