የዓለም ዜና

የሐምሌ 9 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜና


Listen Later

በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ደጋ ዳሞት ወረዳ ፈረስ ቤት ከተማ ትናንት በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ መካከል ከፍተኛ ውጊያ እንደነበር ተሰማ።
እራሱን እስላማዊ መንግሥት የሚለው ጽንፈኛ ቡድን አባላት መሆናቸው የተጠረጠ 82 ግለሰቦችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የብሔራዊ የስለላና የደኅንነት አገልግሎት ዐሳወቀ።
በአፋር ክልል አፍዴራ ከተማ ትናንት ምሽት የጣለዉ ብርቱ ንፋስ የቀላቀለ ዝናብ ለአንድ ሰዉ ሕይወት መጥፋት ምክንያት ሆነ፤ 31 ሰዎችም ተጎዱ። በሺህዎች የሚቆጠሩም ተፈናቅለዋል።
የኬንያ መንግሥት ለበርካታ የአፍሪቃ እና የካሬቢያን ሃገራት የይለፍ ፈቃድ መስፈርቶችን አነሳ።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW