*በቱርክ ፕሬዝዳንት ረቺብ ጣይብ ኤርዶኻን አሸማጋይነት አንካራ ውስጥኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በመካከላቸው የተፈጠረውን ውዝግብ ለለመፍታት «ቴክኒካዊ ውይይት» ለማድረግ መስማማታቸው ተገለጠ ።
*ከአንድ ዓመት የእስር ጊዜ በኋላ ባለፈው ሳምንት የተለቀቁት የቀድሞ የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንደዓ ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ ከማረሚያ ቤት ውጪ በራሳቸው ፍርድ ቤት ቀረቡ ።
*የራስ ገዟ ሶማሊላንድ አዲስ ፕሬዚደንት አብዲራሕማን ሞሐመድ አብዱላሂ ዛሬ ሀርጌሳ ውስጥ ቃለ መሐላ ፈጸሙ ።
*ሣዑዲ ዓረቢያ እንደ ጎርጎሪዮስ አቆጣጠር በ2034 የዓለም ዋንጫን ለማስተናገድ ተመረጠች ።