DW Amharic- በዛሬው የዓለም ዜና ህወሓትን ለሶስት ወራት ከፖለቲካዊ እንቅስቃሴ መታገዱ፣በአማራ ክልል ዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር 40ሺህ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸው፣ሳልሳይ ወያነ ትግራይ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነትን ያፈራረሙ አካላት ጦርነቱን ተከትሎ ለተፈናቀሉ ዜጎች እንዲደርሱ ጥሪ ማቅረቡ፣ ሱዳን እና ሩሲያ በቀይ ባህር ጠረፍ የጦር ሰፈር ለማቋቋም ስምምነት መድረሳቸው፣በጀርመኗ ሙኒክ ከተማ በተሰበሰበ ሕዝብ መካከል መኪና በመንዳት ቢያንስ 28 ሰዎች መጎዳታቸው፣የሩሲያው ፕሬዚዳንት ብላሚር ፑቲን የሩሲያ ዩክሬን ጦርነትን ለማስቆም ለድርድር ተስማምተዋል ሲሉ ዶናልድ ትራምፕ መግለፃቸው አካቷል።