በኢትዮጵያ የፀጥታ እና የፖለቲካ ጥያቄዎች መልስ ካላገኙ ቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ ምርጫ ሊሆን አይችልም ሲሉ የኦፌኮ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ለዶቼቬለ ተናግረዋል። በደቡብ ወሎ ዞን ሐይቅ እና ዉጫሌ ከተሞች አቅራቢያ የተጠለሉ ተፈናቃዮች አቤቱታ አቅርበዋል። እናት ፓርቲ ፣ከተጣመርኩበት «ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት» ከተባለው ቅንጅት፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰርዞኛል ሲል ወቅሷል። እነዚህና የአውሮፓ ኅብረት አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ዛሬ ያካሄዱት ስብሰባ የዛሬው የዜና መጽሔት ዝግጅታችን የሚያተኩርባቸው ጉዳዮች ናቸው።