በአዲስ አበባ ሊካሔድ ታቅዶ የነበረውን ጦርነት የሚቃወም ሰልፍ “የከለከሉ አካላት ተጠያቂ” ሊሆኑ እንደሚገባ የሰላም ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ታዬ ደንደአ አሳሰቡ። ግብጻውያን ከዛሬ ጠዋት 3:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሬዝዳንታቸውን ለመምረጥ ድምጽ ሲሰጡ ዋሉ። እስራኤል ፍልስጤማውያንን ከጋዛ ገፍቶ የሚያስወጣ ፖሊሲ በጦርነት እየተገበረች ነው ሲሉ የዮርዳኖስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አይማን ሳፋዲ ወነጀሉ። እስራኤል ግን ውንጀላውን አስተባብላለች። ጦርነቱ ዛሬ 65ኛ ቀኑን ሲያስቆጥር ከብርቱ ውጊያ በኋላ የእስራኤል ታንኮች ከኻን ዩኒስ ማዕከል መድረሳቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል።