የዓለም ዜና

የሕዳር 4 ቀን 2017 የዓለም ዜና


Listen Later

-የሶማሊላንድ ሕዝብ የወደፊት ፕሬዝደንቱን ለምረጥ ዛሬ ድምፅ ሲሰጥ ዉሏል።በምርጫዉ ራስዋን የሶማሊላንድ ሪፐብሊክ ብላ የምትጠራዉን ግዛት ላለፉት ሰባት ዓመታት የመሩት ፕሬዝደንት ሙሴ ቢሒ አብዲ ከዋነኛዉ ተቃዋሚ ፓርቲ ዕጩ ከአብዲረሕማን መሐመድ አብዱላሒ ጋር በቅርብ ርቀት ይፎካከራሉ።----የእስራኤል ጦር ዛሬም እንደመሰንበቻዉ የጋዛ ሠርጥንና የሊባኖስ ርዕሰ ከተማ ቤይሩትን ሲደበድብ ዋለ።--ባኩ-አዘር በጃን በተያዘዉ የዓየር ንብረት ጉባኤ ላይ የአየር ንብረትን በመበከል ቀዳሚዉን ሥፍራ የሚይዙ ሐገራት መሪዎች ባለመገኘታቸዉ ጉባኤዉ ለአግባቢ ዉጤት መድረሱ እያነጋገረ ነዉ።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW