-በትግራይ ክልል ከሚገኘዉ ከኢሮብ ወረዳ 60 በመቶ የሚሆነዉ አካባቢ አሁንም በኤርትራ ወታደሮች ቁጥጥር እንደሚገኝ የወረዳዉ ነዋሪዎች አስታወቁ። በጋምቤላ ክልል ማንነታቸዉ በዉል ያልታወቁ ታጣቂዎች በከፈቱት ጥቃት ሰላማዊ ሰዎችን ገደሉ።-የአዲስ አበባ መስተዳድር በከተማይቱ የተለያዩ አካባዎች የሚገኙ መንደሮችንና ቤቶችን በጥድፊያ ማፍረሱን ነዋሪዎችና ነጋዴዎች ተቃዋሙ።ቅሬታ አቅራቢዎቹ እንደሚሉት መስተዳድሩ አንዳድ አካባቢዎች የሚገኙ ቤቶቹን የሚያፈርሰዉ አንድም ያለምንም፣ ሁለትም ባጭር ጊዜ ማስጠንቀቂያ ነዉ።