-የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ ሥልጣን በያዙበት ወቅት የነበረዉ የሠላም፣የዲሞክራሲና የመልካም አስተዳደር ቃልና ተስፋ እየሟሸሸ መምጣቱ በሰፊዉ እየተነገረ ነዉ።ጠቅላይ ሚንስትሩ ሥልጣን ከያዙ ዛሬ 7ኛ ዓመታቸዉን ደፈኑ።ኢትዮጵያ ዉስጥ የጋዜጠኞች የመሥራት ነፃነትና ደሕንነት አሁንም አስጊ ነዉ።-የእስራኤል ጦርጋዛ ሰርጥ ላይ በከፈተዉ የዓየር ጥቃት በትንሹ 40 ፍልስጤማዉያን ተገደሉ።ጀርመን ደቡባዊ ጋዛ ራፋሕ ዉስጥ ሰሞኑን የተገደሉት የሕክምና ባለሙያዎች አሟሟት እንዲጣራ ጠየቀች።-ምያንማርን በመታዉ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ3000 በለጠ።