-የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመኖሪያ ቤት አከራይና ተከራዮችን ሚዛናዊ በሆነ መንገድ ያገለግላል ያለዉን አዲስ ሕግ አፀደቀ።ምክር ቤቱ «የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥርና አስተዳደር አዋጅ» ያለዉ ሕግ በአከራይ፣ በተከራይና በመንግስት መካከል ግልፅነትና ተጠያቂነትን ለማስፈን ይረዳል ተብሏል።
-የእስራኤል ጦር ለጋዛ ሕዝብ ርዳታ የሚሰጡ ሠራተኞችን መግደሉን የሐገሪቱ ጠቅላይ ሚንስትር አመኑ።ጥቃቱን የተለያዩ መንግስታትና ድርጅቶች አዉግዘዉታል።በሌላ በኩል ደማስቆ-ሶሪያ የሚገኘዉ የቆንስላ ፅሕፈት ቤቷ ትናንት የጋየባት ኢራን እስራኤል ለመበቀል ዛተች።የዜናዉ መልዕክት የእስካሁኑ ነበር።