-የኢትዮጵያ መንግስት ጦር ኃይል በአማራ ክልል አድርሶታል ተብሎ የሚጠረጠረዉን የጦር ወንጀል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እንዲያጣራ ሁዩማን ራይትስ ወች ጠየቀ።የመብት ተሟጋቹ ድርጅት እንደሚለዉ የመንግስት ወታደሮች አማራ ክልል መራዓዊ ከተማ ዉስጥ በርካታ ሰላማዊ ሰዎች ገድለዋል።ሶማሊያ ዛሬ በሞቃዲሾ የኢትዮጵያን አምባሳደር አባርራለች።ግጭትና ጥቃት ያልተለየዉ የኦሮሚያ ክልል መንግሥት የ30 ዓመታት ጉዞን የሚያሳይ ያለውን የሦስት ቀናት አውደ ርዕይ ከትናንት ጀምሮ በማካሄድ ላይ ነው።