የዓለም ዜና

የመጋቢት 27 ቀን 2016 ዓም የዓለም ዜና


Listen Later

ትናንት ጠዋት በምዕራብ ጎጃም ዞን ፍኖተ ሰላም ከተማ በዳሞት መሰናዶ ትምህርት ቤት ውስጥ በተጣለ ቦምብ 31 ተማሪዎች መቁሰላቸው ተሰማ።
ከምሥራቅ ወለጋ ዞኖች ተፈናቅለው ደብረብርሀን በመጠለያ ስፍራ ቆይተው የተመለሱ ዜጎች ወደ ገጠር ቤታቸው ገብተው መሥራት እንዳልቻሉ አመለከቱ።
የዓለም ባንክ ከኢትዮጵያ ጋር የ1,7 ቢሊየን ዶላር ብድር መፈራረሙን የፋይናንስ ሚኒስቴር አስታወቀ። የፓሪስ ክለብ አበዳሪ ሃገራትም ለኢትዮጵያ የሰጡትን የጊዜ ገደብ እስከ ሰኔ መጨረሻ ማራዘማቸው ተነገረ።
እራስ ገዞቹ ፑንትላንድ እና ሶማሊላንድ የሶማሊያ መንግሥት የቆንስላ ጽሕፈት ቤቶች እንዲዘጉ ያስተላለፈውን ውሳኔ እንደማይቀበሉ አስታወቁ።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW