የመጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
እሥራኤልና አሜሪካ ዛሬ በኢራን ላይ በፈጸሙት ጥቃት ከ25 ሰዎች በላይ ተገደሉ። ከመካከላቸው የኢራን ፈጥኖ ደራሽ አብዮታዊ ዘብ የስለላ ክፍል ሃላፊ ሜጀር ጀነራል ማጃድ ክሀዴሚ ይገኙበታል። በሌላ በኩል ዛሬ በእሥራኤል ላይ ዛሬ ከኢራን ከሂዝቦላ እና ከየመን በተመሳሳይ ጊዜ ጥቃቶች ተፈጽመውባታል
ኢራንና ዩናይትድ ስቴትስ ለ45 ቀናት የተኩስ አቁም እንዲያደርጉና የሆርሙዝ ሰርጥም እንዲከፈት የቀረበውን ረቂቅ ምክረ ሃሳብ ኢራን እንደማትቀበለው አስታወቀች
የናይጀሪያ ጦር ት ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በተፈፀሙ ሦስት ጥቃቶች ቢያንስ 26 ሰዎች መገደላቸውን አስታወቁ ።